አሥራት የማይከፍሉ ክርስቲያኖች ለምን ድሀ እንደሚሆኑ . . . እ...
()
About this ebook
ይህ ጥንታዊ የመስጠት ግንዛቤ አይሁዳውያኖችን ወደ ታዋቂ ሐብት ያደረሳቸው ቢሆንም እንኳን ብዙ ሰዎች ከአሥራት መክፈል አስተሳሰብ ጋር ይታገላሉ፡፡ በዚህ መጽሓፍ ውስጥ ቢሾፕ ዳግ ሂዋርድ ሚልስ አሥራት መክፈል እንዴት አድርጎ ሐብትን ለማፍራትና የብልጽግናን ተአምራት እንደሚያጠንክር ያስተምረናል፡፡ ከዳግ ሂዋርድ ሚልስ ምርጥ ርዕሶች አንዱ በሆነው በዚህ መጽሐፍ ተባረክ፡፡
Dag Heward-Mills
Bishop Dag Heward-Mills is a medical doctor by profession and the founder of the United Denominations Originating from the Lighthouse Group of Churches (UD-OLGC). The UD-OLGC comprises over three thousand churches pastored by seasoned ministers, groomed and trained in-house. Bishop Dag Heward-Mills oversees this charismatic group of denominations, which operates in over 90 different countries in Africa, Asia, Europe, the Caribbean, Australia, and North and South America. With a ministry spanning over thirty years, Dag Heward-Mills has authored several books with bestsellers including ‘The Art of Leadership’, ‘Loyalty and Disloyalty’, and ‘The Mega Church’. He is considered to be the largest publishing author in Africa, having had his books translated into over 52 languages with more than 40 million copies in print.
Read more from Dag Heward Mills
The Art of Leadership: 3rd Edition Rating: 5 out of 5 stars5/5Those Who Forget Rating: 5 out of 5 stars5/5Bible Memorisation Handbook Rating: 5 out of 5 stars5/5Ministerial Barrenness Rating: 5 out of 5 stars5/5Tell Them: 120 Reasons Why You Should Be a Soul Winner Rating: 4 out of 5 stars4/5The Mega Church: 2nd Edition Rating: 5 out of 5 stars5/5What it Means to be as Wise as a Serpent Rating: 5 out of 5 stars5/5Wisdom Is the Principal Thing for Your Ministry Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsChurch Growth Rating: 5 out of 5 stars5/5The Art of Following Rating: 4 out of 5 stars4/5Model Marriage Rating: 4 out of 5 stars4/5Handbook Of Ceremonies Rating: 4 out of 5 stars4/5The Anointed and His Anointing Rating: 5 out of 5 stars5/51000 Micro Churches Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsFruitfulness Rating: 5 out of 5 stars5/5Demons And How To Deal With Them Rating: 5 out of 5 stars5/5Anagkazo - Compelling Power! (2nd Edition) Rating: 5 out of 5 stars5/5
Related to አሥራት የማይከፍሉ ክርስቲያኖች ለምን ድሀ እንደሚሆኑ . . . እ...
Related ebooks
የቤተ ክርስቲያን እድገት Rating: 5 out of 5 stars5/5True Leader Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsWhy Non-Tithing Christians Become Poor and How Tithing Christians Can Become Rich Rating: 3 out of 5 stars3/5Breakthrough Teachings and Prayers: Volume 1 Rating: 0 out of 5 stars0 ratings15 BASIC BIBLICAL KEYS TO POVERTY: If you know what causes it, you can avoid it. Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsThe 10 Win Commandments: Destined to Do Great Things Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsSex, Lies and Your Soul Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsLet My People Go: True Story of How to Overcome Sexual Perversion. Rating: 5 out of 5 stars5/5Conquering Your Financial Worries Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsTemptation: 50+ Tips: Christian Theology Series Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsBlack Hopelessness Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsHoly Ways to Wealth: A Biblical Guide for Wealth Creation Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsBlack Hopelessness Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsExperience Victory in Life by Recognizing Your Enemy and Knowing Your God Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsMarriage Covenant 12 Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsThe Seed of Triumph: Equipping for Life's Victories Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsPrayers for Marriages in Distress Rating: 0 out of 5 stars0 ratings"Backsliding, Am I Still Saved?" Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsIwo Amene Amakusiya Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsScam: Satan Coming After Me: A Book Written to Christians for All People Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsHow Can I Say Thanks Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsUnfold Mysteries Behind Prayer: Knowing the Mysteries Behind Your Prayer Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsA Pathway to Victory Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsThose Who Leave You Rating: 5 out of 5 stars5/5Secrets to Reaching Your Destiny: How to Overcome the 7 Major Challenges in Life Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsIn a Hurry to Be Holy: Short Devotionals for Busy People Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsThrone of Grace: One Man's Journey of Faith and the Power of Prayer Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsRiding in Prosperity: Breaking Forth into the Realm of Supernatural Abundance Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsForgiveness Made Easy (3rd Edition) Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsIwo Amene Amaiwala Rating: 0 out of 5 stars0 ratings
Christianity For You
Winning the War in Your Mind: Change Your Thinking, Change Your Life Rating: 5 out of 5 stars5/5The 5 Love Languages: The Secret to Love that Lasts Rating: 4 out of 5 stars4/5The Purpose Driven Life: What on Earth Am I Here For? Rating: 4 out of 5 stars4/5The Bible Recap: A One-Year Guide to Reading and Understanding the Entire Bible Rating: 5 out of 5 stars5/5The Good Girl's Guide to Great Sex: Creating a Marriage That's Both Holy and Hot Rating: 4 out of 5 stars4/5The Book of Enoch Rating: 4 out of 5 stars4/5Your Brain's Not Broken: Strategies for Navigating Your Emotions and Life with ADHD Rating: 5 out of 5 stars5/5The Screwtape Letters Rating: 4 out of 5 stars4/5The Holy Bible (World English Bible, Easy Navigation) Rating: 4 out of 5 stars4/5Don't Give the Enemy a Seat at Your Table: It's Time to Win the Battle of Your Mind... Rating: 5 out of 5 stars5/5Mere Christianity Rating: 4 out of 5 stars4/5How to Lead When You're Not in Charge: Leveraging Influence When You Lack Authority Rating: 4 out of 5 stars4/5The 21 Irrefutable Laws of Leadership: Follow Them and People Will Follow You Rating: 4 out of 5 stars4/5Law of Connection: Lesson 10 from The 21 Irrefutable Laws of Leadership Rating: 4 out of 5 stars4/5Boundaries Updated and Expanded Edition: When to Say Yes, How to Say No To Take Control of Your Life Rating: 4 out of 5 stars4/5Warrior of the Light: A Manual Rating: 4 out of 5 stars4/5The Story: The Bible as One Continuing Story of God and His People Rating: 4 out of 5 stars4/5Girl, Wash Your Face: Stop Believing the Lies About Who You Are so You Can Become Who You Were Meant to Be Rating: 3 out of 5 stars3/5I'll Start Again Monday: Break the Cycle of Unhealthy Eating Habits with Lasting Spiritual Satisfaction Rating: 4 out of 5 stars4/5The Four Loves Rating: 4 out of 5 stars4/5Boundaries Workbook: When to Say Yes, How to Say No to Take Control of Your Life Rating: 4 out of 5 stars4/5The Unseen Realm: Recovering the Supernatural Worldview of the Bible Rating: 5 out of 5 stars5/5Uninvited: Living Loved When You Feel Less Than, Left Out, and Lonely Rating: 4 out of 5 stars4/5Changes That Heal: Four Practical Steps to a Happier, Healthier You Rating: 4 out of 5 stars4/5Less Fret, More Faith: An 11-Week Action Plan to Overcome Anxiety Rating: 4 out of 5 stars4/5Boundaries with Kids: How Healthy Choices Grow Healthy Children Rating: 4 out of 5 stars4/5Anxious for Nothing: Finding Calm in a Chaotic World Rating: 4 out of 5 stars4/5
Reviews for አሥራት የማይከፍሉ ክርስቲያኖች ለምን ድሀ እንደሚሆኑ . . . እ...
0 ratings0 reviews
Book preview
አሥራት የማይከፍሉ ክርስቲያኖች ለምን ድሀ እንደሚሆኑ . . . እ... - Dag Heward-Mills
አሥራት የማይከፍሉ ክርስቲያኖች ለምን ድሀ እንደሚሆኑ . . . እና አሥራት የሚከፍሉ ክርስቲያኖች እንዴት ሀብታም መሆን እንደሚችሉ
ዳግ ሂዋርድ ሚልስ
ካልተገለፀ በቀር፣ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉ ጥቅሶች ሁሉ የተወሰዱት በ1954 ዓ.ም. ከታተመው የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ነው።
Find out more about Dag Heward-Mills
Healing Jesus Crusade
Write to: evangelist@daghewardmills.org
Website: www. daghewardmills.org
Facebook: Dag Heward-Mills
Twitter: @EvangelistDag
ISBN: 978-1-68398-124-4
ላይትሃውስ ቻፕል ኢንተርናሽናል
መ.ሳ ቁጥር 15134
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
መታሰቢያነቱ
ለ ዶክተር ቻርልስ ኦሴይ
የግል ጓደኛዬ ስለሆንህና በዓመታት መካከል ከጎኔ ስለቆምህ አመሰግንሃለሁ።
ይህንን መጽሐፍ በሙሉም ሆነ በከፊል ያላሳታሚው ፈቃድ ማባዛት የተከለከለ ነው።
ማውጫ
አሥራትየማይከፍሉለምንድሀእንደሚሆኑስድስትምክንያቶች
አሥራትየማይከፍሉትንየሚከተሉእርግማኖች
እግዚአብሔርንመስረቅምንማለትእንደሆነ
አሥራትየማይከፍሉሰዎችሃያመንፈሳዊችግሮች
በገንዘብ ወደ ጥቅም አልባነትየሚያወርዱሰባትእርምጃዎች
አሥራት የማይከፍሉ ሰዎች ያሏቸው መጥፎ ሃሳቦች
እግዚአብሔርንለሚረሱናአሥራትለማይከፍሉየተነገሩትንቢታዊማስጠንቀቂያዎች
እያንዳንዱክርስቲያንስለአሥራትማወቅየሚገባውሰባትነገሮች
እግዚአብሔርየአሥራትንሥርዓትለምንእንደመሠረተ
ሰባትፈር ቀዳጅአሥራት ከፋዮች
የአይሁድ ታሪካዊሀብት
የአይሁድሀብትምስጢራት
ዘመናዊውራባይስለብልጽግናሲያስተምር
አሥራትከፋዮችየሀብትፈጠራሕጎችንእንዴትእንደሚያሟሉ
አሥራትከፋዮችየመዝራትንናየማጨድንሕጎችእንዴትእንደሚቀሰቅሱ
አሥራትከፋዮችእንዴትእግዚአብሔርቤትእንዲሠራላቸውእንደሚያደርጉ
አሥራትከፋዮችእንዴትየእግዚአብሔርንቸርነትእንደሚቀሰቅሱ
አሥራት ከፋዮችእንዴትምጽዋትመስጠትንእንደሚያነሣሡ
አሥራትከፋዮችበሕይወታቸውእንዴትሰማያትንእንደሚከፍቱ
አሥራትንበምትከፍልበት ማናቸውም ወቅትሁሉየሚሆኑአሥርነገሮች
አሥራትን መክፈል ለምን የአገልግሎት የመጀመሪያ እርምጃ እንደሚሆን
አሥራትለአንዳንድሰዎችየማይሠራላቸውአሥርምክንያቶች
ክፍል 1
አሥራት የማይከፍሉ ክርስቲያኖች ለምን ድሀ እንደሚሆኑ
ምዕራፍ 1
አሥራት የማይከፍሉ ለምን ድሀ እንደሚሆኑ ስድስት ምክንያቶች
አሥራት የማይከፍሉ ድሀ የሚሆኑት ምንም የሚሰበስቡት መከር ስለሌላቸው ነው።
ነፋስን ዘርተዋል፣ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ፡ አገዳ የለውም፣ ከፍሬውም ዱቄት አይገኝም ቢገኝም እንግዶች ይበሉታል።
ሆሴዕ 8፡7
የብልጽግና መሠረታዊ ቅርጹ የአንድ ሰው ዘርን መዝራትና በኋላም በምላሹ መከርን መሰብሰቡ ነው። አሥራትን አለመክፈል አንድን ሰው ከዚህ መሠረታዊ የመዝራትና የማጨድ መርህ ውጭ ያደርገዋል። አሥራትህን ሳትከፍል ስትቀር የብልጽግናህን መሠረቶች ስለምትንድ የገንዘብህን አቋም ትጎዳለህ።
አሥራት የማይከፍሉ ድሀ የሚሆኑት በረከቶችን ወደ ሕይወታቸው ስለማይስቡ ነው።
በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ፥ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፦
ሚልክያስ 3፡10
አሥራት መክፈል የእግዚአብሔር ቃል እንደሚናገረው የተለያዩ ዓይነት በረከቶችን ይስባል። የተባረከ ሰው ሞገስና ረድኤት ያገኘ ሰው ነው። የምድር ሕይወታችን በጣም አስቸጋሪ ነው። ፈርዖን ዕድሜህ ምን ያህል ነው?
ብሎ ያዕቆብን ስለ ሕይወቱ በጠየቀው ጊዜ እንዲህ አለ፣ ያዕቆብም ለፈርዖን አለው። የእንግድነቴ ዘመን መቶ ሠላሳ ዓመት ነው። የሕይወቴ ዘመኖች ጥቂትም ክፉም ሆኑብኝ፥ አባቶቼ በእንግድነት የተቀመጡበትንም ዘመን አያህሉም
(ዘፍጥረት 47፡9)።
ኢዮብም እንደዚሁ የሰው ልጅ ዕድሜ ጥቂትና በመከራ የተጨናነቀ መሆኑን ተናገሯል። በሕይወትህ ምንም ዓይነት መርገም ባይኖርብህም እንኳ ብዙ ችግሮችና መከራዎች ይገጥሙሃል። አሥራትህን ሳትከፍል ስትቀር በሕይወት ውስጥ የሚንሰራፉትን ችግሮች የሚቋቋምልህን በረከት ታጣለህ። መከራ ባንዣበበት ኑሮህ ላይ ምንም ዓይነት የበረከት ቃል ካልፈሰሰ እንዴት መሻሻል ትችላለህ? አሥራት የማትከፍል ሆነህ በሕይወትህ ላይ የድህነት ክምር ቢጫንብህ አይድነቅህ። አሥራት በሚከፍል ሰው ላይ ባለጸጋ የሚያደርግና ሐዘንን የሚያርቅ በረከት በብዛት ይመጣለታል።
አሥራት የማያወጡ ድሀ የሚሆኑት የተረገሙ ስለሆኑ ነው።
ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው።
እናንተ፥ ይህ ሕዝብ ሁሉ፥ እኔን ሰርቃችኋልና በእርግማን ርጉሞች ናችሁ።
ሚልክያስ 3፡8-9
አሥራት በማይከፍሉ ሰዎች ላይ የተለየ እርግማን አለ። ይህ እርግማን በዓለም ላይ ከሚታወቁ ታላላቅ ሃያ አምስት እርግማኖች አንዱ ነው። ይህ እርግማን አሥራት በማይከፍሉ ሰዎች ላይ ከሚፈሰሱት ከአዳም፣ ከኖኅና ከሌሎች ትውልዶች ተላልፎ ከመጡት እርግማኖች ላይ ተጨማሪ ነው። አሥራት በማይከፍሉ ሰዎች ላይ የሚመጣው እርግማን በወላጆችህና በቀደምት አባቶችህ ላይ በደረሰውና በተወላጆቻቸው ላይም በተላለፈው እርግማን ላይ በመደረብ ይሠራል። ሁላችንም በአንድም ሆነ በሌላ ምክንያት ከሠሩት ነገሮች የተነሣ የተረገሙ ሰዎች ተወላጆች ነን ማለት ያስደፍራል።
አንድ ቀን፣ ቀደምት አባቶቼ የባሪያ ፈንጋዮች እንደነበሩ ስደርስበት በጣም ተጨነቅሁ። ለባሪያ ንግድ የተመሠረተ ጥንታዊ ወደብ በአባቴ ከተማ መኖሩንም ደረስሁበት። ከዚህም የተነሣ እኔ ለምርኮ ካልተሸጡ ሰዎች የአንዱ ተወላጅ መሆኔ ግልጽ ነው። ስለዚህም እኔ ወንድሙን ለባርነት አሳልፎ የሸጠ የአንድ ሰው ተወላጅ መሆኔ የሚያስኬድ ነገር ነው። ወንድምህን አሳልፎ መሸጥ በእርግጥ በቤተሰብህ ውስጥ እርግማንን ያመጣል። ወንድሞቻቸውን ለመስተዋትና ለርካሽ ጌጣጌጥ አሳልፈው የሸጡ ሰዎች የሚኖሩባቸው ቦታዎች ዛሬ በዓለም ላይ ለምን በድህነት አረንቋ የሚማቅቁ እንደሆነ ጠይቀህ አታውቅም?
በመሆኑም አሥራትን አለመክፈል በሕይወትህ ላይ ከእነዚህ እርግማኖች ላይ ተጨማሪ እርግማንን ያስከትላል። ቀድሞውንም በአዳም እርግማን ምክንያት እየተሠቃየህ እንዳለህ አትዘንጋ። በተጨማሪም የካም ተወላጅ ከሆንህ ደግሞ በካም እርግማን ምክንያትም እየተጎሳቆልህ ትሆናለህ።
ወድ ወዳጄ ሆይ፣ ከዚህ በላይ ምን ያህል መሸከም ትችላለህ? በረከትን የሚያመጣ አንድን ነገር ለማድረግ አሁን ጊዜው አይመስልህም? እነዚህን ሁሉ ጠንቀኛ እርግማኖች እንድትቋቋም የአሥራት መክፈልን በረከት ማግኘት ያስፈልግሃል! ታዲያ አሥራትህን ለመክፈል እምቢ ባልህ መጠን የባሰ እየደኸየህ መሆንህ የሚያስገርም ነውን?
አሥራት የማይከፍሉ ድሀ የሚሆኑበት ምክንያት ነቀዞች ያለማቋረጥ ሀብታቸውን ስለሚበዘብዟቸው ነው።
ስለ እናንተ ነቀዙን እገሥጻለሁ፥ የምድራችሁንም ፍሬ አያጠፋም
በእርሻችሁም ያለው ወይን ፍሬውን አያረግፍም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፦
ሚልክያስ 3፡11
አሥራት መክፈል የሚያስገኘው ከፍተኛ በረከት እግዚአብሔር ለአንተ ነቀዙን መገሠጹ ነው። የድሀ አገሮች መሪዎች ሲናገሩ ከሰማሃቸው ትንሽ ተጨማሪ ገንዘብ ቢያገኙ ችግራቸው ሁሉ እንደሚወገደላቸው ከአባባላቸው ትረዳለህ። ነገር ግን እውነቱ ይህ አለመሆኑ ያሳዝናል። እስካሁን ድረስ እንኳ በዓይነተኛ ድህነት የሚማቅቁት ብዙ የገንዘብ ድጋፍ የሚቀበሉ አካባቢዎች ናቸው። ይህ እንቆቅልሻዊ ገጽታ የሚታየው የገንዘቡ ተቀባዮች የተሰጣቸውን ገንዘብ ለመያዝ ባለመቻላቸው ነው።
ቀዳዳ ያለበትን ባልዲ ለመሙላት የሚያስፈልግህ ምን እንደሆነ አስበህ ታውቃለህ? ሀብት ውኃ የተሞላ ባልዲ ሆኖ ፍቺ የሚሰጠው ቢሆን፣ እንዲህ ያለውን ባልዲ ለመሙላት የሚያስፈልግህ ውኃ ብዙ በሆነ ነበር። ነገር ግን ቀዳዳዎቹ ከተደፈኑ ባልዲውን ለመሙላት የሚያስፈልግህ ትንሽ ውኃ ብቻ ነው።
ይህ ነቀዙ ከተገሠጸ በኋላ የሚገኝ ምስጢራዊ በረከት ነው። ነቀዙ ከተገሠጸ በኋላ አንተን ሀብታም ለማድረግ የሚያስፈልግ ነገር ቢኖር ጥቂት ነገር ብቻ ይሆናል። ይሁንና እንዲህ ዓይነቱ በረከት ከሌለህ የተሻሉ ሥራዎችን ብትፈልግም፣ ከዚያም የተሻለ ገንዘብ ብታገኝም፣ ነገር ግን ሁልጊዜም ሀብታም መሆን አይሳካልህም። ነቀዙ ከተገሠጸ ያን ያህል አታገኝ ይሆናል ነገር ግን ባልዲዎችህ በፍጥነት ይሞላሉ። ከዚያም ወዲያው ሞልተው መፍሰስ ይጀምራሉ።
ውድ ወዳጄ አሥራትህን በምትከፍልበት ጊዜ እግዚአብሔር ሊያደርግልህ የገባው ተስፋ ይህ ነው። ዛሬውኑ ከድህነትህ ውጣና ነቀዙ ከተገሠጸ በኋላ የሚመጣውን በረከት ተቀበል። ሰዎች በመካከለኛው ዕድሜያቸው ለምን ትልቅና ወፍራም እንደሚሆኑ ጠይቀህ ታውቃለህ? ሰዎች ብዙ ጊዜ በዚህ ዕድሜ አብዝተው አይበሉም። እንደ እውነቱ ከሆነማ በመካከለኛ ዕድሜ ያሉ ብዙ ሰዎች ክብደታቸውን ለመቀነስ ምግብ ይቀንሳሉ። እንዲህም አድርገው ክብደታቸው ይጨምራል። ይህ የክብደት መጨመር ምክንያቱ ምንድን ነው? ሰዎች ዕድሜአቸው እየጨመረ ሲሄድ የበሉትን ምግብ ለሰውነት አገልግሎት የመለወጥ ዓቅማቸው ያሽቆለቁላል። በሌላ አነጋገር ስብን የሚያቃጥለው እሳት ያንሳል ማለት ነው። በሰውነት ውስጥ ስብን የሚያቃጥለው እሳት በየቀኑ አስር ልኬቶችን ያቃጥል ከነበረ ወደ አምስት ያዘቀዝቃል እንደ ማለት ነው።
ከዚያም በድንገት በየቀኑ ያልተቃጠለ አምስት ልኬት ስብ በሰውነትህ ውስጥ መከማቸት ይጀምራል። ያለ ምንም ጥረት ክብደት ትጨምራለህ፣ እየሰፋህ እየሰፋህም ትሄዳለህ። የአንድን ሰው ዕድሜ በሰውነቱ መጠን የምታውቀው ለዚህ ነው። እያረጀህ ስትሄድ ንጥረ ምግብን ለሰውነት አገልግሎት የመለወጡ ሂደት እየቀነሰ ይሄዳል (ነቀዙ ተገሥጾአል)፣ የክብደት ጭመራውም (ብልጽግናው) መከሰት ይጀምራል።
በእርግጥ አሥራት የማይከፍሉ እየደኸዩ የሚሄዱበት ምክንያት በቁጥጥር ሥር ያልዋለ ነቀዝ በሕይወታቸው ስስላለ ነው።
አሥራት የማይከፍሉ የሚደኸዩት የማሳቸው ፍሬዎች ያለማቋረጥ ስለሚጠፉ ነው።
ስለ እናንተ ነቀዙን እገሥጻለሁ፥ የምድራችሁንም ፍሬ አያጠፋም በእርሻችሁም ያለው ወይን ፍሬውን አያረግፍም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፦
ሚልክያስ 3፡11
በብክነት፣ ሥርዓት በጎደለው አያያዝ፣ በግዴለሽነት፣ በእሳት፣ በአደጋዎች፣ በዓመፆች፣ በስርቆትና በጦርነትም ያፈራኸውን ያለ አግባብ ማጣት ጎጂ ቢሆንም ይህ በእርግጥ የአጥፊው ሥራ ነው። አሥራት የመክፈል በረከቶች ከሆኑት አንዱ ነቀዙ መገሠጹ ነው። አጥፊው የነቀዙ ወንድም ነው። በነቀዙና በአጥፊው መካከል ያለው ልዩነት አጥፊው ሀብትህን በሚጎዳ ሁኔታና በጭካኔ ማስወገዱ ነው። የሀብትህ አጥፊ በአንተ ላይ ሲሠራብህ ማየት እጅግ ያማል። ምክንያቱም በእንዲህ ዓይነት የሚገጥምህን ጥፋት ለመቀበል ትርጉም አልባ ሆኖ ስለሚሰማህ ነው። አሥራትህን መክፈል ጀምር፣ እግዚአብሔር የሀብትህን አጥፊ እንደሚገሥጽ ተስፋ ገብቷል።
አሥራት የማይከፍሉ ክርስቲያኖች ድሆች የሚሆኑት መከራቸውን ለመሰብሰብ ዕድል ከማግኘታቸው በፊት ፍሬዎቻቸውን ስለሚነጠቁ ነው።
ስለ እናንተ ነቀዙን እገሥጻለሁ፥ የምድራችሁንም ፍሬ አያጠፋም በእርሻችሁም ያለው ወይን ፍሬውን አያረግፍም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፦
ሚልክያስ 3፡11
አሥራት የማይከፍሉ ክርስቲያኖች የሚደኸዩበት ሌላኛው ምክንያት የመከራቸውን ፍሬ ለመሰብሰብ ዕድል ከማግኘታቸው በፊት ስለሚጠፋባቸው ነው። አሥራት የማይከፍሉ የጠፋ መከር
እርግማን አለባቸው። የጠፋ መከር የሚያሳየው ላፈሰስኸው ቅሪት ተመጣጣኝና ተገቢ መከርን መሰብሰብ አለመቻልን ነው።
የሆነ ሰው ጠንክረህ ብትሠራ ሀብታም ትሆናለህ እያለ በልበሙሉነት ያስተምር ነበር። በመቀጠልም፣ ሀብታም ያልሆኑ ሰዎች ጠንክረው የማይሠሩ ናቸው። በማደግ ላይ ያሉ አገሮች ወገባቸውን ታጥቀው መሥራት ይገባቸዋል፣ ያን ጊዜ ብልጽግና ዕድል ፈንታቸው ይሆናል
በማለት ተናገረ።
ነገር ግን ዞር ብለህ ብታይ፣ ላባቸውን እያንጠፈጠፉ የሚሠሩ ሰዎችን ትመለከታለህ። ሆኖም ግን እነዚህ ሰዎች ሀብታሞች አይደሉም! ራሳቸው እስከሚዞር በየቀኑ ለአሥራ ሁለት ሰዓት የሚሠሩ ሰዎችን ታገኛለህ። የሚያገኙት ገቢ ግን ባዶ ለማለት እስከሚያስደፍር መናኛ ነው። ከእነዚሁ ሰዎች ጥቂት ራመድ ብለህ ብትመለከት ደግሞ ለአንድ ሰዓት ብቻ እየሠሩ ሚሊዮኖችን የሚያፍሱትን ትመለከታለህ።
አዎን ተግቶ መሥራት ወደ ብልጽግና መምራት እንደሚገባው እውነት ነው። ይሁን እንጂ በአመዛኙ ይህን ሲያስከትል አይታይም። በስዊድን አገር የሚገኝ የአውቶብስ አሽከርካሪ በጋና ያለ ተመጣጣኝ ባለሙያ የሚያገኘውን አስራ ዘጠኝ እጥፍ ያገኛል። ይህ ለምን ይሆናል? ላጠፉት አንድ ዓይነት ሰዓትና ላከናወኑት አንድ ዓይነት ሥራ ለምን እኩል አያገኙም? ለምንድን ነው አንዱ አንድ መቶ ዘርቶ አንድ መቶ ሲያገኝ ሌላኛው ደግሞ አንድ መቶ ዘርቶ ሃያ ሦስት የሚያገኘው?
በእርግጥ የጠፉ መከሮች የቱ ጋር እንዳሉ የምታየው እዚህ ላይ ነው። የባከነ መከር ማለት አንድ ሰው ላፈሰሰው ቅሪት ተመጣጣኙን መከር ማግኘት ሳይችል ሲቀር ነው። ብዙ ሰዎች እንዲህ ዓይነቱ የቡቃያ መርገፍ ሰለባዎች ይሆናሉ።
ብዙ ጊዜ የቡቃያ መርገፍ መንስኤዎች መከሩ ከጠፋበት ሰው ቁጥጥር ውጭ ናቸው። አንድ ሜክስካዊ ሰው ከድንበሩ አምስት ማይሎች አለፍ ብሎ ከሚኖረው አሜሪካዊ አቻው ለልፋቱ በጣም ያነሰ የሚያገኘው ለምንድን ነው? በአሜሪካ ምድር ያለ አሜሪካዊ አቻው የሜክሲካዊውን ያህል ጊዜና ጥረት አድርጎ ከሜክሲካዊው አስራ ዘጠኝ ጊዜ የበለጠ ውጤት የሚያገኘው ለምንድን ነው? ለዚህ እቆቅልሽ መንስኤዎቹም ይሁኑ መፍትሄዎቹ ግለሰቡ ለማስተካከል ከሚችለው በላይ ናቸው። ነገር ግን ሁሉን ቻይ አምላክ መከሩ ያለአግባብ ወደ መሬት እንደማይወድቅበት ለአሥራት ከፋዩ ሰው ተስፋ ገብቶለታል። ፍሬዎችህ ከመከሩ ጊዜ በፊት እንዲረግፉ አይፈቅድም። አሥራት መክፈል ለብልጽግና ዋነኛው ቁልፉ መሆኑ ታዲያ ለምን ይደንቃል? አሥራት የማይከፍሉ ከገቢያቸው አሥር ከመቶውን ለእግዚአብሔር ከመስጠት በመከልከላቸው ድሀ ሊሆኑ መቻላቸው ያስደንቅሃልን?
ያለ እግዚአብሔር እርዳታ ምን ማድረግ ትችላለህ? እግዚአብሔር ካልረዳህ በቀር ምንስ ያህል ርቀህ መሄድ ትችላለህ? ልትጠቀምባቸው ሳትችል በመቅረትህ ፍሬዎችህ ወደ መሬት ከመርገፋቸው በፊት አሁን አሥራት መክፈል መጀመር ግድ ነው።
ምዕራፍ 2
አሥራት የማይከፍሉትን የሚከተሉ እርግማኖች
አሥራቶችን አለመክፈል በርካታ የተለያዩ እርግማኖችን ይቀሰቅሳል። ብዙ ሰዎች አሥራትን አለመክፈል የሚቀሰቅሰው "የሚልክያስ