ሰይመው! ይገባኛል በል!! ውሰደ!!!
5/5
()
About this ebook
ይህ በጌታ የተሰጠ ማረጋገጫ ለዚህ አዲስ እና ኃይለኛ መጽሐፍ “ሰይመው፣ ይገባኛል በል፣ ውሰድ!” መሰረት ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ፣ ቢሾፕ ዳግ ሂዋርድ-ሚልስ አማኙ መንፈሳዊ፣ አካላዊ እና ቁሳዊ መጣስ እንዲሆንለት የሚያስችለውን ዋነኛ ቁልፍ ያሳያሉ፡፡
Dag Heward-Mills
Bishop Dag Heward-Mills is a medical doctor by profession and the founder of the United Denominations Originating from the Lighthouse Group of Churches (UD-OLGC). The UD-OLGC comprises over three thousand churches pastored by seasoned ministers, groomed and trained in-house. Bishop Dag Heward-Mills oversees this charismatic group of denominations, which operates in over 90 different countries in Africa, Asia, Europe, the Caribbean, Australia, and North and South America. With a ministry spanning over thirty years, Dag Heward-Mills has authored several books with bestsellers including ‘The Art of Leadership’, ‘Loyalty and Disloyalty’, and ‘The Mega Church’. He is considered to be the largest publishing author in Africa, having had his books translated into over 52 languages with more than 40 million copies in print.
Related to ሰይመው! ይገባኛል በል!! ውሰደ!!!
Related ebooks
እግዚአብሔርን ማገልገል ትልቅ ነገር ነው Rating: 4 out of 5 stars4/5የሚከሱህ ሰዎች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsወደኋላ ማፈግፈግ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsዝንጉዎቹ Rating: 5 out of 5 stars5/5ዛፉ እና አገልግሎትህ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsበየቀኑ ከእግዚአብሔር ጋር ውጤታማ የጥሞና ጊዜ ሊኖርህ ይችላል Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsመልካም ጄነራል Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsላይኮስ ተኢው ስው እር አንልግኤት Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsልጄ ሆይ ትችያለሽ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsትእቢተኞች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsበዕብራውያን ላይ የተሰጡ ስብከቶች (I) - እምነታችሁን እንዴት ማጠንከር ትችላላችሁ? Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsዳግም መወለድ ብሎም ገሃነምን ማስወገድ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsየጥንቱ ወንጌል ጥበብ (Amharic53) Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsትተውህ የሚሄዱ ሰዎች Rating: 2 out of 5 stars2/5ጣፋጭ የመንፈስ ቅዱስ ተፅዕኖዎች Rating: 4 out of 5 stars4/5መንፈሳዊ አደጋዎች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsመጽሐፍ ቅዱስህን አንብብ በየቀኑ ጸልይ Rating: 5 out of 5 stars5/5አስመሳዮቹ Rating: 3 out of 5 stars3/5ቤተ ክርስቲያን ትከል Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsሌሎች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsየተቀባው ሰው እና ቅባቱ Rating: 5 out of 5 stars5/5ወደ ቅባቱ የሚያደርሱ እርምጃዎች Rating: 5 out of 5 stars5/5አገልግሎትህን አጉላው በመንፈስ ቅዱስ በሚደረግ ተዓምራትና መገለጦች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsአደገኞች ልጆች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsየትህትና ቀመር Rating: 5 out of 5 stars5/5ቅባቱን ያዝ Rating: 5 out of 5 stars5/5ታማኝነት እና ታማኝ አለመሆን Rating: 2 out of 5 stars2/5መጽሐፍ ቅዱስን በልብ ለማስታወስ ማጥኛ መጽሐፍ Rating: 5 out of 5 stars5/5የድል ሚስጢር Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsእረኛ መሆን ምን ማለት ነው Rating: 5 out of 5 stars5/5
Reviews for ሰይመው! ይገባኛል በል!! ውሰደ!!!
2 ratings0 reviews
Book preview
ሰይመው! ይገባኛል በል!! ውሰደ!!! - Dag Heward-Mills
ሰይመው! ይገባኛል በል!! ውሰደው!!!
ዳግ ሂዋርድ ሚልስ
ትርጉም፡- ብስራት ተክሌ
አርትዖት፡- ዘላለም ፀጋዬ እና መጋቢ ልዑል ኃይሉ
ካልተገለፀ በቀር፣ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉ ጥቅሶች ሁሉ የተወሰዱት በ1954 ዓ.ም. ከታተመው የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ነው።
Find out more about Dag Heward-Mills
Healing Jesus Crusade
Write to: evangelist@daghewardmills.org
Website: www. daghewardmills.org
Facebook: Dag Heward-Mills
Twitter: @EvangelistDag
Write to:
Dag Heward-Mills
P.o.Box 114
Korle-Bu
Accra
Ghana
ላይትሃውስ ቻፕል ኢንተርናሽናል
ስልክ +251912063821
መ.ሳ ቁጥር 15134
አዲስ አበባኢትዮጵያ
ISBN: 978-1-61395-443-0
ይህንን መፅሐፍ በሙሉም ሆነ በከፊል ያላሳታሚው ፈቃድ ማባዛት የተከለከለ ነው።
ማውጫ
የስኬት ዋነኛ ቁልፍ
እውነተኛ የሆነ እምነት ማዳበር
ሰይመው!
‘‘የእኔ ነው’’ በል!
ነኝ! አለኝ! እችላለሁ!
እንዴት እንደምትወርሰው
በተግባር ‘‘የእኔ ነው’’ ማለትና አዎንታዊ የስምምነት ቃል!
ምዕራፍ 1
የስኬት ዋነኛ ቁልፍ
ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል . . .
ዕብራውያን 10፡38
‘‘ሰይመው! ይገባኛል በል! ውሰደው!
ምን ማለት ነው;
‘‘ሰይመው፣ የእኔ ነው በል፣ እናም ውሰደው’’ የሚለው አነጋገር በአጭሩ እምነትን ስለመተግበር ይገልጻል። ሁሉም ክርስቲያን እምነት ሊኖረውና ሊለማመደውም ይገባል። እምነት በሕይወታችን የመጣስና የተአምራት ምክንያት ነው። እምነት የጸሎታችን መልስ ምክንያት ነው! በአጠቃላይ እምነት ያላቸው ሰዎች በተቃራኒው እምነት ከሌላቸው የበለጠ ባለጠጎች ናቸው። እኔ በእምነትና ያለ እምነት በሚራመዱ ክርስቲያኖች መካከል ያለውን ልዩነት አይቼአለሁ።
የእምነት ሰዎችም እንደሌላው ሰው ይበሳጫሉ፣ ይታመማሉ እንዲሁም ሌሎች ነገሮች ያጋጥሟቸዋል። ነገር ግን በአጠቃላይ እነርሱ ላይ ያስተዋልሁት ነገር በረከትን፣ መበልጸግን እንዲሁም ረጅም ዕድሜን ነው።
ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።
ዕብራውያን 10፡38
ከእምነት ወደ ኋላ ብታፈገፍግ እርሱ በአንተ እንደማይደሰት እግዚአብሔር በቃሉ ተናግሯል። እምነት ብዙም ጠቃሚ አይደለም ብለው የሚያስቡ አሉ። እነዚህ ሰዎች ከእምነት ሰዎችና ስለ እምነት ከሚነገረው መልእክት ይሸሻሉ። በክርስትና ሕይወታቸውም የበለጠ ትኩረት መስጠት ያለባቸው ለትዕግሥት፣ መረጋጋትና ቅድስና ለመሳሰሉት እሴቶች እንደሆነ ያስባሉ። በእርግጥ በክርስትና ሕይወታችን ከተጠቀሱት ነገሮች ወደ ኋላ ማለት አለብን ማለት አይደለም። ልብ የሰውነታችን በጣም ጠቃሚ ክፍል ነው ስንል ኩላሊት አይጠቅምም ማለት አይሆንም፤ ሁለቱም ጠቃሚ ናቸው። ምክንያቱም ሁለቱም ለሰውነታችን የተለያየ ሚና ይጫወታሉ።
እምነት በእያንዳንዱ ሰው የክርስትና ሕይወት ላይ በጣም ልዩ እና ጠቃሚ ሚና አለው። መጽሐፍ ቅዱስም ያለ እምነት እግዚአብሔርን ማስደሰት የማይቻል መሆኑን ይነግረናል።
ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና።
ዕብራውያን 11፡6
የእግዚአብሔር ቃል ያለ ፍቅር እግዚአብሔርን ማስደሰት አይቻልም አይልም። ያለ ሰላም እግዚአብሔርን ማስደሰት አይቻልም ተብሎም አልተጻፈም።
መጽሐፍ ቅዱስ እውነታውን ግልጽ አድርጎልናል። ያለ እምነት እግዚአብሔርን ማስደሰት አይቻልም!
አብርሃም በእግዚያብሔር ላይ የነበረው እምነት ጽድቅ ሆኖ ተቆጥሮለታል። አብርሃም ኤልሻዳይ የሆነው አምላክ በእርጅና ዘመኑ ልጅ እንደሚሰጠው አምኖ ተቀብሏል። አብርሃም የራሱ ድክመቶች ነበሩት። ስለ ሚስቱ ዋሽቷል። እንዲሁም ሚስቱን አማኝ ላልሆኑ ነገሥታት አሳልፎ ሰጥቷል። ምንም እንኳ ቢዋሽም ሆነ ቢያመቻምችም አምላኩ በተናገረው ቃል ላይ እምነት ስለነበረው እግዚአብሔር በእርሱ ተደስቷል።
ምናልባት በአንተ መመዘኛ አብርሃም ፈተናውን አላለፈ ይሆናል። ይሄኔ በአንተ አስተያየት አብርሃም ጥሩ ሰው አልነበረም። በእግዚአብሔር እይታ ግን አብርሃም ታላቅ ሰው ነበር። ታላቅነቱም የእምነቱ ውጤት ነው።
ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። ስለዚህ ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት።
ሮሜ 4፡21፣ 22
ውድ ክርስቲያን ወዳጄ፣ እግዚአብሔር ደስተኛ የሚሆነው ስታምነው ነው። እግዚአብሔር ይፈውሰኛል ብለህ ስታምን ደስተኛ ታደርገዋለህ! እግዚአብሔር እንደሚያበለጽግህ ስታምን፣ እግዚአብሔርን ደስተኛ ታደርገዋለህ። ነገሮችህን ጥሰህ የምትወጣው በቅርብ ጊዜ እንደሆነ ስታምን እግዚአብሔር ይደሰታል። ረጅም እድሜ እኖራለሁ ብለህ ስታምን